• Bylaw Amendment

    ለአሪዞና አንድነት መረዳጃ እድር አባላት በሙሉ፣

    የአሪዞና አንድነት መረዳጃ እድር የቀድሞ ኮሚቴ በMarch 30, 2024 ቀን ጠርቶ በነበረው የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ከታች በቀረቡት ጉዳዮች ላይ ድምጽ ሊሰጥበት ተስቦ የነበረ ቢሆንም በጊዜ ገደብና በሌሎች ምክንያቶች የተነሳ በሁሉም የሕግ ማሻሻያዎች ላይ ድምፅ መስጠት አልቻልንም ። የኮሚቴው አባላት በእነዚህ ማሻሻያዎች ላይ ምርጫችሁን ለማግኘት አማራጭ ቴክኖሎጂዎችን (ቴሌግራም ጣቢያ) ለመጠቀም ሞክረዋል። ቢሆንም ግን ከአባላቱ መካከል ግማሽ የሚያህሉት የእድሩን የቴሌግራም ገጽ ላይ አልተመዘገቡም ። ስለሆነም ተቀባዪ ኮሚቴ February 1 ቀን 2025 ዓ.ም ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራ ወስኗል። ኮሚቴው የሚሻሻሉትን ሕጎች ከዚህ በታች በዝርዝር አቅርቧል:: እያንዳንዱ አባል ማሻሻያውን በማንበብና በማወቅ በ February 1, 2025 በሚደረገው ስብሰባ ላይ ድምፅ ለመስጠት ዝግጁ ሆኖ መምጣት ይጠበቅበታል። በቀረቡት  ማሻሻያዎች  ላይ February 1,2025 ዓ.ም በተገኙት አባላት የመጨረሻ ውሳኔ እንደሚሰጥ ከወዲሁ  ኮሚቴው በትህትና  ያሳስባል። 

    የእድሩ ኮሚቴ ከዚህ በታች በተዘረዘሩት 18 ጉዳዮች ላይ ድምፅ እንዲሰጥ ሐሳብ አቅርቧል። 15 ከቀረቡት ሃሳቦች ውስጥ የድሩን ሕግና  ደንብ ማሻሻያ እና 3 ሀሳቦች የእድሩን  የገንዘብ ሁኔታ ለማሻሻል የቀረቡ ናቸው::

     ስለተሳትፎዎ  እናመሰግናለን::

    የእድሩ  ኮሚቴ

    የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያዎች

    To all Arizona Andnet Meredaja Edir Members:

    Arizona Andnet Meredaja Edir (AAME) held its General Assembly meeting on March 30, 2024. However, due to time limitations and other factors, we were not able to vote on all of the bylaw amendments. The committee members have tried to utilize alternative technologies (Telegram Channel) to get your vote on these amendments. Unfortunately, almost half of the members have not subscribed to the telegram page of the Edir. Therefore, the Edir committee has decided to call a General Assembly on February 1, 2025. The committee is sending the list of bylaws to be amended. Each member is required to read and familiarize themselves with the recommended amendments and come prepared to vote on February 1, 2025. Please be advised that a final decision will be made by the members who are present on February 1, 2025. 

    The Edir committee has proposed to vote on the 18 items listed below. 15 of the proposals are amendments to the Bylaws of AAME and 3 proposals are to improve the financial condition of AAME. Your vote will help determine how the AAME will be managed and have a say on the financial matters of the AAME.

    Thank you for your participation!

    Edir Committee

    Bylaw Amendments

  • የሻምበል ባሻ ገብረስላሴ ሕልፈተ ሕይዎት

    ለአሪዞና አንድነት መረዳጃ እድር አባላት በሙሉ፣

    የእድራችን አባል የሆኑት የሻምበል ባሻ ገብረስላሴ ገዳን ሕልፈተ ሕይዎት አስመልክቶ በ1/2/25 ከእድሩ 15,000 ዶላር ወጭ ተደርጏል። ይህን ወጭ ለመተካት፣ እያንዳንዱ አባል $35 እንዲከፍል ተወስኗል:: በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 10.1 እና አንቀጽ 10.2 መሰረት ከ 1/28/25 እስከ 2/27/25 $35.00 ያለመቀጫ፣ ከ2/28/25 እስከ 3/15/25 ደግሞ ከ$25.00 መቀጫ ጋር $60.00 እንዲከፍሉ በትህትና እናሳስባለን:: በዚህ ጊዜ ክፍያውን ያልከፈለ አባል ቢኖር በመተዳደሪያ ደንቡ አንቀጽ 10.2 እና 10.3 መሰረት፣ ከእድሩ የወጡ መሆኑን ልናሳውቅ እንወዳለን።

    የክፍያ መንገዶች፦

    1. በ Online ለመክፈል azedir.org ላይ Make Payment የሚለውን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ

    2. በ Zelle ለመክፈል የARIZONA ANDINET MEREDAJA EDIR ስልክ ቁጥር የሆነውን 623-499-0428 ይጠቀሙ። በZelle ክፍያ የሚፈጽሙ ከሆነ ሙሉ ስምዎትንና የአባል መለያ ቁጥርዎትን፤ ለሌላም አባል የሚከፈሉ ከሆነ የአባሉን ስምና የአባሉን መለያ ቁጥሩን በማስታወሻ ሳጥን (Memo Box) ውስጥ እንዲጽፉ በአክብሮት እንጠይቃለን።

    3. በቀጥታ ባንክ ማስገባት ከፈለጉ የ ዌልስ ፋርጎ ባንክ አካውንታችንን Account Number 7330133609 እና Routing Number 122105278 ይጠቀሙ። የከፈሉበት ደረሰኝ ላይ ስምዎትን ጽፈው ፎቶ በማንሳት 623-499-0428 ላይ ቴክስት እንዲያደርጉ በትህትና እናሳስባለን።

    4. በጥሬ ገንዘብ ለመክፈል ባቲ ባዛር እና የእናት እንጀራ ሱቆች መክፈል ይቻላል።

    ስለአባልነትዎ እናመሰግናለን
    የእድሩ ኮሚቴ

    To All Members of Arizona Andnet Meredaja Edir

    The Edir has disbursed $15,000 on 1/2/2025 to cover funeral expenses of our member Ato Gebreselassie Geda. As outlined in the Bylaws of the Edir, this expense shall be allocated to the remaining qualifying and active members. Accordingly, it was decided that each member’s contribution will be $35.00. We kindly request that each active member pay $35.00 from 1/28/2025 to 2/27/2025 without penalty and $60.00 including a penalty of $25.00 from 2/28/2025 to 3/15/2025 in accordance with Article 11 of the Bylaws.
    Please note that per Article 11 of the bylaws of the Edir, members who do not complete the required payment within the mentioned time frame will forfeit their membership status.

    Here are the available payment methods:

    1. To pay online on azedir.org using a debit/credit, Click the link Make Payment on this page.
    2. To pay via Zelle, use Arizona Andnet Meredaja Edir’s phone number 623-499-0428. Please make sure to enter your full name and member ID number in the memo box. If you also pay for another member, please enter the member’s full name and member’s ID number in the memo box.
    3. To make a direct deposit into the Edir’s Wells Fargo Bank Account, please use Account Number 7330133609 and Routing Number 122105278. Please write your name on your deposit receipt and send a picture to 623-499-0428.
    4. To pay by cash, make the payment at Bati Bazar and Yenat Injera Market

    We appreciate your membership!
    AZ Andnet Meredaja Edir Committee